ይህ የምዝገባ ቅፅ አዲስ 'የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ትውልድ' (New Generation of Human Rights Defenders - NGHRDs) በሚል የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሚያመቻቸው ሥልጠና ላይ ለመሳተፍ የተዘጋጀ ቅፅ ነው። ሥልጠናው በየዓመቱ የሚካሔድ ሲሆን ፍላጎቱ ያላቸው ተማሪዎች ሰብዓዊ መብቶች ላይ ያላቸው ዕውቀት እንዲጨምር በማሰብ የተሰናዳ ነው። የሥልጠናው ተሳታፊ ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻቸው እና በማኅበረሰባቸው ዘንድ አሳሳቢ በሆኑ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው እንዲሟገቱ እና ለሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ማኅበራዊ መሠረት እንዲገነቡ ይጠበቃሉ።
በዚህ ሥልጠና ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ይህንን ቅፅ መሙላት ይጠበቅባችኋል።
ማሳሰቢያ፤ የምንሰጠው ሥልጠና ለውሱን ተሳታፊዎች ብቻ ስለሆነ ሥልጠናው ላይ አንዲገኙ የሚገልጽ ግብዣ የደረሳቸው ተሳታፊዎች ብቻ በሥልጠናው ላይ የሚገኙ ይሆናል።
ይህ ቅፅ የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ለሚማሩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ብቻ ነው።