አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካሁ
የተክበራችሁ ወንድም እህቶች ተማሪዎች፤
እውቀት ከንግገርም ከስራም መቅደም አለበት አይደል ....?
እነሆ ከፊታችን ያለውን የረመዷንን ወር ጾም ከመጀመራችን በፊት ስለጾም ሙሉ ትምህርት ተምረን ጾማችንን በልማድ ሳይሆን በቁርአንንና በትክክለኛው ሃዲስ አስተምህሮት ይሆን ዘንድ፤ የጾም ህግጋቶች ስልጠና ይዘን ብቅ ብለናል፤
>>ስልጠናው የሚሰጠው በሸይኻችን በሸይኽ ሙሐመድዘይን ዘህረዲን ኸሊል
>>>ትምህርቱ የሚጀመረው (ሻእባን 10 -23 ፣ ) ይሆናል
>>ትምህርቶቹ የሚተላለፈው በፊስቡክ እና ዩቱዩብ በቴሌግራምም ይለቀቃል
>>ስልጠናውም ከ13-15 ቀን በተከታታይ ይሰጣል፤
>>በቀን አንድ ትምህርት ከነመልመጃ ጥያቄዎች ፤
>>ስልጠናው ሙሉ ለሙሉ በነጻ፤
>>>ትምህርቱን ላጠናቀቀ የመጨረሻ ፈተና ይሰጣል በዛም መሰረት የምስክር ወረቀት (ሰርተፍኬት ይሰጣል)
ከርሶ ምን ይጠበቃል፤
1. በግዜ መመዝገብ በቴሌግራም እንዲሁም ዩቱብ ላይ አባል መሆን
2. በያለኡበት ሁነው በ24 ሰአት ውስጥ 1 ሰአት በመስጠት ግዜዎን ማመቻቸት
3. ትምህርቶችን ተከታትለው አስፈላጊውን ማስታወሻ መያዝ
4. ያልገባዎትን ጉዳይ በአካባቢዎ ከሚገኙ አሊሞች እና ኡስታዞች መጠየቅ ለኛም ቢሆን በተቻሉበት አጋታሚ መጠየቅ
5. የመልመጃ ጥያቄዎችን መስራት
6 የመጨረሻ ፈተና በሰኣቱ መፈተን እና ሰርተፍኬቶን መውሰድ
7 ጾሞትን በተማሩት ትምህርት መሰረት ለመጾም መታገል
8 ለወንድም እህቶ የተማሩትን ትምህርት ማስተላለፍ